(Read this post in English.)

የመማክርት ፓናላችን አባላት ኤሪን እና አልስቴይር የሁለት ሳምንታት የክትትል ጉብኝት በአዲስ አበባ ያደርጋሉ።

ባለፈው ዓመት የሙዚቃ ቴራፒስቶቻችን ኤማ ብሪተን እና ኤሪን ዊሊያምስ-ጆንስ በአዲስ አበባ ለአራት የተለያዩ የእንክብካቤ መስጫ ተቋማት– ለገፈርሳ የአእምሮ ጤና ማገገሚያ ማዕከል፣ ለፍቅር – የኢትዮጵያ አእምሯዊ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማህበር፣ ለሆስፒስ ኢትዮጵያ እና ለቤዛ የአዕምሮ ህክምና ክሊኒክ የአራት ሳምንታት ፕሮጀክት አካሂደዋል፡ ኤማ እና ኤሪን በጋራ 26 ተንከባካቢዎችን ማሰልጠን እና የተሳትፎ ሠራተኞች የራሳቸውን የሙዚቃ ክፍለ ጊዜ ለመምራት ያላቸውን እምነት ማሳደግ ችለዋል።

በዚህ ወር ኤሪን ከሙዚቃ ቴራፒስት እና ከረጅም ጊዜ የቆዩ መማክርት ፓናል አባል አልስቴይር ሮበርትሰን ጋር በመሆን የሙዚቃ አጠቃቀማቸውንና የወደፊት አቅጣጫቸውን አብረው እንዲመለከቱ ወደ ጋበዟቸው ወደ አራቱም የእንክብካቤ መስጫ ተቋማት ተምልሰው ይሔዳሉ። ኤሪንና አልስቴይር የልፋታቸውን ስኬት ለማክበርና የመስክ አጋሮቻችን በእንክብካቤያቸው ላሉ ሁሉ ሙዚቃን መጠቀማቸውን እንዲቀጥሉ ይረዳናል ብለው ሰለሚያስቡት ማንኛውንም ሐሳብ ምክርና እርዳታ ለመስጠት ጊዜቸውን ይሰጣሉ።

ስለ ሥራቸውና ውሏቸው በየጊዜው የምንለቀውን ዜና እንድትከታተሉ እናሳስባለን። በመቀጠልም ኤሪንና አልስቴይር ሙዚቃን ለእንክባካቤ ለማዋል እንዴት እንደተንሳሱና የሚያመጣውንም ልዩነት ያካፍሉናል።

ሙዚቃ ለእንክብካቤ የሚያነሳሳኝ መደነስ እና መዘመር እንድትችል ማስቻሉ ነው።

Alastair Robertson

ሙዚቃ ለመንከባከብ ስላለው ልዩነት ያነሳሳኝ ምንም ያህል ችሎታ ቢኖረውም በሰዎች መካከል እንደ ቋንቋ እንዴት እንደሚሰራ ነው። የመማር ችግር ካለባቸው ሰዎች ጋር በሙዚቃ በመስራቴ ክብር ይሰማኛል። ደንበኞቼ ጥልቅ ስሜትን ለቤተሰብ አባላት እና ለሌሎች ባለሙያዎች በድምጽ ሲገልጹ ለማየት ችያለሁ። ሙዚቃ ለእነዚህ ስሜቶች ለብዙ ሰዎች ተደራሽ በሆነ መንገድ እንዲካፈሉ ቦታ ይሰጣል ፣ የመማር እክል ያለባቸውን ከሌሎች ጋር እንዲገናኙ ፣ አስተያየቶችን ፣ ሀሳቦችን እና ስሜቶችን እንዲገልጹ ይረዳል ።

Erin Williams-Jones

ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ከሆኑ እና በምትሰጡት እንክብካቤ ውስጥ ሙዚቃ ለመጠቀም ፍላጎት ካላችሁ ወይም ቀደም ሲል በተጋላጭ ሁኔታ ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር በሚሰሩበት ጊዜ ሙዚቃን የተጠቀሙ ከሆነ ከእርስዎ ለመስማት እንወዳለን። እባክዎን የቡድናችን ረዳት የሆነውን ኪራን በ kiransangha@musicastherapy.org በኢሜል ያግኙት።